Monday, 10 June 2013

ታደሰ የኋላእሸት አለምነህ የአሁኑ መላከ ብርሃናት ገብረስላሴ የኋላሸት አለምነህ ማን ነው?

ለምድ የለበሰ አስመሳይ የተኩላ ባህታዊ፤

መግቢያ

የኢትዮጵያ
 ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሁለት ሽህ ዓመት በላይ ታሪክ ያላት ጥንታዊት ቤተክርስቲያን ስትሆን በኢትዮጵያ ታሪክ ዉስጥም ትልቅ ቦታ ይዛ የምትገኝ የታሪክ ደሴት ናት፡፡ ቤተክርስቲያኗ ጥንካሬዋን ጠብቃ የታሪክ ክብርና ሞገስ ሆና እዚህ እንድትደርስ ደግሞ ካህናትና መንፈሳዊ አባቶች የአንበሳዉን ሚና የተጫዉቱ ሲሆን  የቤተክርስቲያንዋ ዋና ምሰሶዎች በመሆን አስተምሮቷን  ሳይሸራርፉና ሳያዛንፉ በታማኝነት እየተቀባበሉ ዘመናትን አሻግረዉ ዛሬ ላይ አድርሰዋታል፡፡ የዛሬወቹ ባላደራወችም ይህንኑ የማስቀጠል ትልቅ መንፈሳዊ አደራ ከምንግዜዉም በላይ ተሸክመዉ ጉዞዉን ጀምሯል፡፡ ሆኖም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በሚያሳዝን ሁኔታ ይችን ዘመናትን ተሻግራ ዛሬ ላይ መቆም የቻለች ቤተክርስቲያን ሊያደናቅፍና ስሟን ጥላሸት ሊቀባ የሚችል ፀያፍ ስራ አንዳንድ መንፈስ ቅዱስ ተገለጠልን በሚሉ በራሷ ሰዎች /ባላደራወች/ ሲፈፀም መታየት ጀምሯል፡፡እንዲህ እያደረግን ያለነው ቤተክርስቲያኗ ምን አይነት ምግባረ ብልሹነትእየተስፋፋባት እንደሆነች ለማሳየት ነው እንጂ እነርሱን በግል ለማሳጣት አይደለም።ይህን መደበቅ እና ማለፉ ጉዳቱ ለቤተ ክርስቲያን እንደሆነ ግልጽ፡ነው። 
ወደዚህ ሰው ታሪክ እንመለስ ታደሰ የኋላ እሸት አለምነህ ማን ነው?



ከዚህ ላይ ደግሞ አሜሪካ የዛሬ 2 እመት መነኮስኩ ብሎ........... መነኩሴ መስሎ ሲቀድስ (ጅብ በማያውቁት ሃገር ሄዶ ቆርበት አንጥፉልኝ ይላል አሉ......ወይ ማጭበርበር)

እንደ ታደሰ አለምነህ የኋላሸት አገላለጽ፤ ወላጆቹ ጋብቻቸውን ፈጽመው "የመጀመሪያ ልጅ ወልደው ደስ ብሏቸው ሳለ፤ ይኸው ልጅ በሕጻንነቱ ሲሞትባቸው፤ አሁንም ሁለተኛ ሲወልዱ ሲሞትባቸው፤ በመጨረሻ ሶስተኛ ልጅ ወልደው አሁንም ሲሞትባቸው" ይኼ የፈጣሪ ቁጣ ነው ብለው ተስፋ በመቁረጥ መኝታ ለይተው ይኖሩ እንደነበር ሁልጊዜ ይተርክልናል።  ታሪኩን በየጊዜው አዲስ ሰው ወደ ሲያትል ገብርኤል በመጣ ቁጥር ለዚያ አዲስ ሰው ስለራሱ ታሪክ ሲያወራ ይደመጣል።  በተጨማሪም እንደ ታደሰ አገላለጽ፤ እናቱ ለፈጣሪዋ ልጅ ከሰጠኸኝ አገልጋይ እንዲሆንህ ላንተ እሰጥሃለሁ እያለች ትሳል ስለነበር፤ እግዚአብሔር ጸሎቷን ሰምቶ አንድ በሃታዊ ከሩቅ ሐገር ከፈጣሪ ተልኮ ወደ ወላጆቹ መኖሪያ በመምጣት ወላጆቹን "እናንተ እስከ መቼ ድረስ አልጋ ለይታችሁ ትኖራላችሁ" ካለ በኋላ ለእናቱ ከእግዚአብሔር እንደተላከና እርሷም የተባረከ እና የተቀደሰ ልጅ ትወልጃለሽ እንዳላትና፤ ልጁም ካደገ በኋላ እናንተን ይጦራችኋል፤ አይዞአችሁ ተጽናኑ ተብለው እንደተነገሩ በራሱ አንደበት ሁልጊዜ ይነግረናል። "ራሱን ያጸደቀ ሰው"…. ምን እንበለው…መልሱን ለእናንተ ለአንባቢያን እተወዋለሁ።  ይህ በእንዲህ እንዳለ  ወላጆቹ ይህን መልእክት ከሰሙ በኋላ፤ ያንን የእግዚአብሔር ሰው ወደቤት ጋብዘው ከሸኙት በኋላ፤ ያችን ዕለት መኝታቸውን አንድ አድርገው አደሩ። በዚያች ሌሊት ታደሰ የኋላእሸት አለምነህ ተጸነሰ (አቤት ውሸት)። በ1949 ዓ.ም በደብረታቦር ፋርጣ ወረዳ ተወለደ። እናቱም ስለቷን ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ስለነበረባት እርሱ (ታደሰ የኋላእሸት አለምነህ) ከተወለደ በሰባት አመቱ ለቤተክርስቲያን እንደተሰጠ ብዙ ጊዜ ሲናገር እንሰማዋለን። ከዚያስ …….
በሚቀጥለው ጽሑፍ ታደሰ የኋላእሸት አለምነህ እንዴት እንደተወለደ ከነሙሉ ታሪኩ ከቤተሰቦቹ ዘንድ ጠይቀን ስለ እርሱ ማንነት ጠንቅቀን አረጋግጠናል፤ በተጨማሪም ታደሰ አግብቷል ወይስ አላገባም? እንዴት አሜሪካ ሊመጣ ቻለ፤ ክህነቱ አለ ወይስ የለም? እነዚህን የመሳሰሉትን ጽሑፍ ይዘን እንቀርባለን  እናንተም ተከታተሉን፤
እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል የሚል የአባቶቻችን እነጋገር አለ…..


ይቆየን….

No comments:

Post a Comment